TG Telegram Group Link
Channel: ያህዌ ንሲ (እግዚአብሔር ዓላማዬ ነው)
Back to Bottom
ዘመኗን በሙሉ በቤተ እግዚአብሔር በዝማሬ ስታገለግል ኖራለች። በአገልግሎትም በእድሜም አሁን በዲላና አካባቢው ለምንገኝ የዝማሬ አገልጋዮች ቀዳሚት አገልጋይ ናት።
ገጠር ከተማ ሳትል ታገለግላለች በተለይም ገጠር አካባቢ ስትጠራ በደስታ ሄዳ ታገለግላለች የሚገርመው "ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" እንዲል ቅዱስ ቃሉ የጎደሉ ንዋዬ ቅድሳትን ገዝታ በማሟላት ለብዙ አገልጋዮች አርአያ የምትሆን አገልጋይ ናት።
ለሰ/ት/ቤት ያላት ፍቅር ልዩ ነውና የዜማ ዕቃዎችን በብዙ አድባራት ገዝታ አበርክታለች። ታላቋ እህታችን ዘማሪት በረከት ደግፌ።
እነሆ አሁን ደግሞ እግዚአብሔር እረድቷት በቤተክርስትያናችን ሥርዓትና አስተምህሮ መሰረት ያዘጋጀችውን የዝማሬ አልበም የፊታችን እሁድ ሰኔ 9/2016 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌ/ኮ/ቡ ሀ/ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሌሎችም የሀ/ስብከታችን ሰራተኞች በተገኙበት በዲላ ዋለሜ ደ/ሰ/ቅ/ዑራኤል ቤ/ክ ስ/ወ/አዳራሽ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በልዩ ድምቀት ልታስመርቅ ዝግጅቷን አጠናቅቃለች ስለሆነም የተዋህዶ ልጆች በስፍራው ተገኝተን በዝማሬ አምላካችንን እናከብር ዘንድ ኑ ብላናለች ስለሆነም ይህ መልዕክት የደረሰን ሁሉ የጥሪ ካርድ አንጠብቅ በዕለቱ ተገኝተን በብፁዕ አባታችን ቡራኬ ፣ በዝማሬውም እየተባረክን እህታችንን እናበረታታ።
ለዚያ ዕለት ያድርሰን !
ለብዙዎች ሼር በማድረግ የእህታችንን አገልግሎት እናግዝ ....
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
ዘመኗን በሙሉ በቤተ እግዚአብሔር በዝማሬ ስታገለግል ኖራለች። በአገልግሎትም በእድሜም አሁን በዲላና አካባቢው ለምንገኝ የዝማሬ አገልጋዮች ቀዳሚት አገልጋይ ናት።
ገጠር ከተማ ሳትል ታገለግላለች በተለይም ገጠር አካባቢ ስትጠራ በደስታ ሄዳ ታገለግላለች የሚገርመው "ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" እንዲል ቅዱስ ቃሉ የጎደሉ ንዋዬ ቅድሳትን ገዝታ በማሟላት ለብዙ አገልጋዮች አርአያ የምትሆን አገልጋይ ናት።
ለሰ/ት/ቤት ያላት ፍቅር ልዩ ነውና የዜማ ዕቃዎችን በብዙ አድባራት ገዝታ አበርክታለች። ታላቋ እህታችን ዘማሪት በረከት ደግፌ።
እነሆ አሁን ደግሞ እግዚአብሔር እረድቷት በቤተክርስትያናችን ሥርዓትና አስተምህሮ መሰረት ያዘጋጀችውን የዝማሬ አልበም የፊታችን እሁድ ሰኔ 9/2016 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌ/ኮ/ቡ ሀ/ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሌሎችም የሀ/ስብከታችን ሰራተኞች በተገኙበት በዲላ ዋለሜ ደ/ሰ/ቅ/ዑራኤል ቤ/ክ ስ/ወ/አዳራሽ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በልዩ ድምቀት ልታስመርቅ ዝግጅቷን አጠናቅቃለች ስለሆነም የተዋህዶ ልጆች በስፍራው ተገኝተን በዝማሬ አምላካችንን እናከብር ዘንድ ኑ ብላናለች ስለሆነም ይህ መልዕክት የደረሰን ሁሉ የጥሪ ካርድ አንጠብቅ በዕለቱ ተገኝተን በብፁዕ አባታችን ቡራኬ ፣ በዝማሬውም እየተባረክን እህታችንን እናበረታታ።
ለዚያ ዕለት ያድርሰን !
ለብዙዎች ሼር በማድረግ የእህታችንን አገልግሎት እናግዝ ....
👇👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
Forwarded from D.N YOHANS YD
https://hottg.com/Dilla_Live



ሼር
ሼርሼር
ሼርሼር
ሼር
ከፍ ካለው በላይ

የመጣው ሄደ፣ የሄደውም አይመጣም። የነገሠው ተሻረ ፣ የተሻረው ዳግም አይቀባም። የተሞገሰው ተረገመ፣ የተወገዘው ስሙ ያው ሆኖ ቀረ ። ባለ ጠጎች ደኸዩ ፣ አለ የሚባል ጠፍቶ ነበር የሚል ቃል በምድር በረከተ። ጎዳናው ይወስዳል ይመልሳል፣ ሕይወት ግን ያንን ጓደኛ፣ ያንን ውብ ዘመን፣ ያንን ክብር፣ ያንን አንቱታ አትመልስም ። በዘመኑ ታላቁ እስክንድር ዓለም ፈራው ፣ ዛሬ ፈሪዎች አይፈሩትም። እግዚአብሔር ማነው ? ያለው ፈርዖን ሰጠመ ፣ እስካሁን ትንሣኤ አላገኘም ። አውሮፓ ዱር ሳለ ግሪክ አሰለጠነች፣ ዛሬ ግሪክ በዕዳ ተዘፍቃ ብዙ ረዳት ሊያቆማት አልቻለም ። የጰጰሱ ተሳሳቱ ሲባል ይወገዛሉ፣ አስኬማና በትረ ሙሴ መልሱ ይባላሉ ።

ቆንጆዎች ቆንጆ ነበርሁ ሲሉ ማን ያምናቸዋል? ያ ውበት ላይመለስ ጥላሸት ተቀብቷል ። ያ ተክለ ቁመና ፣ ያ እንደ ፀሐይ የሚያበራ ገላ ፣ ያ መሬት ለመርገጥ የሚጸየፍ እግር ዛሬ ጭቃ ላይ ተኝቷል ። ቤቱን ለደቂቃ የማያምነው ለዘላለም ጥሎት ሄዷል። የሚሳሳለትን ንብረት ዛሬ የማያውቀው ሰው ይጫወትበታል ። የሕይወት መንገድ መሄጃ እንጂ መመለሻ የለውም ። እኛ ወደ እነርሱ እንጂ እነርሱ ወደ እኛ አይመጡም። የዓለም ከፍታ በዝቅታ ፣ ዙፋን በመቃብር ፣ ዳኝነት በእስረኛነት ይለወጣል ። ያንተን ልዕልና ፣ አማኑኤል ሆይ ያንተን ክብር ካላሰቡ ልብን ያደክማል ።

ከፍታህ ዝቅታ የለውም፡፡ ነበረ ተብሎ ታሪክ አይነገርልህም። ሁልጊዜ ያው ነህ ። እንዳንተ የሸመገለ የለም፤ እንዳንተም አዲስ የለም ። መጀመሪያ ላይ ቆመህ መጨረሻውን ታውቃለህ፤ እያወቅህ ግን ዝም ትላለህ። ለድሀው እንጀራ ትሰጣለህ ፣ መልሶ ሲክድህ የሚያማልድ ሰባኪ ትልክበታለህ ። በልካችን አትከፍለንም ፣ በልክህ ታኖረናለህ ። መሰላል ላይ የወጡ ይወርዳሉ። በአየር ላይ የተንሳፈፉ መሬት ይናፍቃሉ ። ከፍ ካሉት በላይ ከፍ ያልከው አንተ ግን በማይነገር ቅድስና ትኖራለህ ። ለጠባይህ ዝቅታ ፣ ለዙፋንህ መናወጥ የለበትም ። የዛሬው አሸናፊ የሁልጊዜ አሸናፊ አይደለም ። የዛሬው ፈራጅ የሁልጊዜ ፈራጅ አይደለም ። የእኔ አምላክ ግን የማለፍን ሥርዓት ድል ትነሣለህ ። ሳትቀበል ትሰጣለህ ። ሳትሾም ትሾማለህ ። አዎ ከፍ ካሉት በላይ ከፍ ብለሃል ። ልዕልናህን ልዕልናህ ያመሰግናል ። በክረምቱ ዝናብ ነጠብጣብ ልክ ብትመሰገን ልክህ አይደለም ።

በምድር ላይ ያንተ ትልቅ ነገር እኛ ነን ። በሰማይና በምድር የእኛ ትልቅ አንተ ሁንልን ! 

👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
" እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ"
(የሉቃስ ወንጌል 1:19)

  #የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ታቦት በ 1887 ዓ/ም በደጅ አዝማች ባልቻ ሳፎ(አባ ነፍሶ) ፈቃድ ከጎጃም ደብረ ኤልያስ አካባቢ ወደዚህ ታሪካዊ ቦታ እንደመጣና ደብሩ ከተመሰረተም 129 ዓመታትን እንዳስቆጠረ ይነገራል ። በኋላም በ1926 ዓ/ም በራስ ደስታ ዳምጠው ህንፃ ቤተክርስቲያኑ እንደተገነባ የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ።

ቤተክርስትያኑ እጅግ ተራራማ ስፍራ ላይ ያለ ከመሆኑ የተነሳ በአራቱም አቅጣጫ በሩቁ ይታያል። ታዲያ በሩቁ ሲታይ ግርማ ሞገሱ እጅግ ያስደምማል። ወደ ውስጥ ሲገባ ግቢው በአጸዶች ከመሞላቱ የተነሳ ለነፍስ ሀሴት ይሰጣል። ከመግቢያ በሩ ጀምሮ እስከ ህንጻ ቤተመቅደሱ ድረስ የተገነባው ደረጃ ሲወጡት ወደ ሰማይ ወደታላቅ ከፍታ እየወጡ ያለ እስኪመስል ልዩ የደስታ ስሜትን ይፈጥራል። በአርምሞ ነፍስ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገርበትን ሁኔታ የሚፈጥር አንዴ ወደ ውስጥ ከዘለቁ ከቶም "ውጡ ውጡ" የማይል ድንቅ ቦታ ነው።

በዓመት 2 ጊዜ ታህሳስ እና ሐምሌ 19 መጥቶ ያነገሰ ልቡ አርፎ ነፍሱ ሐሴት አድርጋ ፣የሕይወት እንቆቅልሹ ተፈቶ ድንቅ ተዓምራቶችን ተመልክቶ ይመለሳል። በነዚህ ቀናት ተገኝቶ የሚያነግሰው የእምነቱ ተከታይ ብቻ አይደለም ብዙዎች የሌሎች ቤተእምነት ተከታዮችም ሳይቀር ተማጽነውት ልመናቸውም ተፈጽሞ ብዙ ኪ.ሜትሮችን ተጉዘው ስዕለታቸውን ዶሮውን ፣ በጉን ፣ ከብቱን ፣ ዕጣኑን ፣ ጧፉን ፣ ሻማውን ፣ የድባብ ጥላውን ይዘው መጥተው ቅዱስ ገብርኤል ያደረገላቸውን ሲመሰክሩ የሰማ የልቡን ጥያቄ ለተራዳዒው መልዐክ ለመንገር ይቸኩላል፣ በጸበሉም ቢሆን ብዙዎች ካለባቸው ደዌ እየተፈወሱ የሚመለሱበት ድንቅ የፈውስ ቦታ ነው ።
በጌዴኦ፣ ኮሬና ቡርጂ  ሀገረ ስብከት ውስጥ ከሚገኙ ታላላቅ አድባራት መካከል አንዱና ጥንታዊው የጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሲሆን ፣

ከአዲስ አበባ 360 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በድንቅ መልክዐ ምድሩና በደን አጠባበቁ በዩኔስኮ ተመዝግቦ የቱሪስት መዳረሻ በሆነው በጌዴኦ ዞን፣  የዞኑ መዲናና የሰላም ተምሳሌት በሆነችው በለምለሚቷ ዲላ ከተማ  ይገኛል። ዘንድሮም ሐምሌ 19/2016 ታላቁን የቅ/ገብርኤልን ዓመታዊ ክብረ በዓል ለማክበር ጥቂት ቀን ብቻ ቀርቶናል ክብረ ዓሉም  የጌዴኦ ፣ኮሬና ቡርጂ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሆኑት ብፁዕ አቡነ ገሪማ በተገኙበት  ሌሎችም ታላላቅ ሊቃውንተ ቤ/ክ ሰባክያነ ወንጌልና ዘማርያን በተገኙበት በልዩ ድምቀት ይከብራል። እናንተም በዚህ ድንቅ የበረከት ስፍራ ተገኝታችሁ የበዓሉ በረከት ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ ፣ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።  !!

Via ዲ/ን መብዓጽዮን (ኢ/ር)
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል

እግዚአብሔርን ከሚፈራ በቀር ባለጸጋ የሆነ ሰው ማነው? የእውነት እውቀት ከጎደለው ሰው በላይ ፍጹም ደሃ የሆነ ማን ነው? ሁል ጊዜም እውነተኛ ፍቅራችን ጸንቶ ይቀጥል ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ እርሱን ለምነው ስለ ቸርነቱ ምስጋና አቅርብ ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል፡፡

              [ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ]

@Yahiwenesei
ለድሆች መጽውቱ

"እውነተኛ ሐሴት ትፈልጋላችሁን? እንግዲያውስ ለድሆች መጽውቱ፤ ክርስቶስን ወደ ቤታችሁ ጥሩት ይህን ስታደርጉ ማዕዱ ቢነሳም ሐሴቱ አይነሳም ይቀጥላል እንጂ።

           [ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]

@Yahiwenesei
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሐምሌ 19/2016 ዓ/ም ጪጩ ገብርኤል አይቀርም
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
+++ ሠርካችሁን(አመሻሹን )ማለዳ የሚያደርግ ጌታ አለ +++

በብዙ ነገሮች ባለ ድል አይደለሁም ፣ ውጥኔ አልተሳካልኝም ፣ ምኞቴ ምኞት ሆኖ ቀረ፣ የበዪ ተመልካች ነኝ ፤ የዕድሜዬ አስኳል፣ የሥራው ጊዜ አለፈ ካላችሁ ፣ ፀሐይን በገባዖን ሰማይ ያቆመ፣ ሠርካችሁን ማለዳ የሚያደርግ ጌታ አለ! ማንም እንዳይቋቋመን አድርጎ የብረት አጥር ይሆንልናል።

👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
🌻 በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል🌻
(መዝሙረ ዳዊት 65:11)

ተመግበን የኖርነው በቸርነቱ ነው። የተደገፍንባቸው ሁሉ ተሰብረው ገሚሶቹም እንደሸምበቆ ወግተውን ያልወደቅነው በቸርነቱ ነው። የሚዝቱብን በዝተው ያልጠፋነው በቸርነቱ ነው። "አለቀለት/ላት/" እየተባልን እንደገና አዲስ የሆነው በቸርነቱ ነው። ያለ ቀልባችን ሁነን ስንበርና ስንዋከብ አደጋውን ያለፍነው በቸርነቱ ነው።
በረሃብ ዘመን በልተን ያደርነው በቸርነቱ ነው። ተምረን የተመረቅነው፣ ነግደን ያተረፍነው፣ ተናግረን የተሰማነው ፣አግብተን የወለድነው ፣ ወልደንም የሳምነው፣ አርሰን የሰበሰብነው ፣በፊቱ ለአገልግሎት የቆምነው በቸርነቱ ነው። ጊዜአችንን በኃጢአትና በበደል ጭርስ አድርገን ደግሞ እንደገና ለንስሃ ዘመን የተቀዳጀነው በቸርነቱ ነው።
ለዚህ ያደረሰን ቸር አምላካችን እግዚአብሔር እናመሰግነዋለን🙏🙏🙏 !!!
እንኳን አደረሳችሁ🙏🌻😍 !!!
👇👇👇👇👇👇
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
@Yahiwenesei
HTML Embed Code:
2024/09/27 12:23:52
Back to Top