23 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በዩናይትድ ስቴትስ እየተካሔደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የሮቦፌስት ውድድር ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡
አብርሆት ቤተ-መፃሕፍት ከአቦጊዳ የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ማዕከል ጋር በመተባበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ በውድድሩ እየተሳተፉ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
በዩናይትድ ስቴትስ ሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሔደ በሚገኘው ውድድር 23 ታዳጊዎች ኢትዮጵያን ወክለው በተለያዩ ዘርፎች እየተሳተፉ እንደሆነ ታውቋል።
ግንቦት 5/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር፤ ኢትዮጵያውያኑ ታዳጊዎቹ የሚያሸንፉ ከሆነ በሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ለመቀጠል የሚያስችላቸውን ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚያገኙ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
>>Click here to continue<<