TG Telegram Group Link
Channel: TIKVAH-ETHIOPIA
Back to Bottom
#ኢትዮጵያ

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች አንድ አባት  በጎረምሶች ተከበው ሲመቱ ፣ ሲሰደቡ ፣ ሲዘለፉ ፣ ሲዋከቡ በቪድዮ ታይቷል።

ይህን እጅግ አሳፋሪና በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለን ሚያሳይ ቪዲዮ ያጋሩት ደግሞ እራሳቸው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ናቸው።

ድርጊቱ ብዙዎችን ክፉኛ አስቆጥቷል። በርካቶች ስለ ነገ በማሳብ ፍርሃት ውስጥ ከቷቸዋል።

በእርግጥ በሀገራችን ያላየነው ግፍ ፣ ያልሰማነው ክፉ ተግባርና ጭካኔ ምን አለ ? እንዘርዝር ብንልስ ቦታው፣ ጊዜው  ይበቃናል ? በፍጹም !

ከዚህ በፊትም እንደምንለው በቪዲዮዎች ተቀርጾ የምናየው ምናልባትእድለኞች ሆነን ከብዙ አንዱ እንጂ ስንት ያላየነው ይኖራል።

ወደ ቪድዮው ስንመለስ ተከበው ሲመቱ፣ ሲዋከቡ ፣ ሲዘለፉ የነበሩት አባት ' እንጀራ ፍለጋ እግር ጥሏቸው እንደመጡ ' ይገልጻሉ የሚጠይቀን የለም ባዮች ጎረምሶች ' እዚህ አካባቢ ምን ትሰራለህ ? ለምን እዚህ መጣህ ? ከመጣህበት ቦታስ እንጀራ የለም ? ' ሲሉ እጅግ በንቀት ያዋክቧቸዋል።

ይህን ተግባራቸውን እንደ በጎ ስራ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አጋርተውታል።

የትኛውም ዜጋ በገዛ ሀገሩ የመንቀሳቀስ መብት አለው ? ካልሆነ ስለምን #ኢትዮጵያዊ ይባላል ? ጥፋት ካለበት ፣ ከተጠረጠረ የሚጠይቀው ህግ እንጂ የሰፈር ጎረምሳ አይደለም። ግለሰቦቹ ጥርጣሬ አለን ካሉ ህግን ማሳወቅ እንጂ ማነው ፤ የትኛው ህግ ነው ይህንን መብት የሰጣቸው ? 

ይህ ተግባር በተለይ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተነዛ ያለው የጥላቻ ስብከት ምን ያህል ስር እንደሰደደ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን ነገን እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል።

ግልጽ የሆነ የብሄርና የግለሰቦች ጥላቻ ፣ ልብም አእምሮም በጥላቻ መሞላት፣ አይንም በጥላቻ መታወር ፦
- ሌላው ይቅር ታላላቆቻችን እንዳናከብር
- ለእምነታችን ፣ ለሃይማኖታችን ቦታ እንዳይኖረን
- ለሰው ልጅ ትንሽ እንኳን ቦታ እንዳንሰጥ
- ለህግ እና ስርዓት ቅንጣት ታክል ደንታ እንዳይኖረን
- ባህል፣ ወግ ፣ አብሮነት ለሚባለው ጉዳይ ቦታ እንደሌለን
- ነገ እኔስ ምን ይገጥመኛል ? ምን እሆን ይሆን ? በህይወት አጋጣሚ የት እሄዳለሁ ፣ ምን አካባቢ እገኛለሁ የሚለውን ለማገናዘብ እንኳን እንዳንችል ያደርገናል።

ሰዎች ወደው ሳይሆን በስርዓት፣ በግለሰቦች፣ በአንቂዎች ፣ በሚዲያዎች... አማካኝነት ነው ጥላቻ እንዲውጣቸው እና ማገናዘብ ፣ ቆም ብሎ ማሰብ የሚባለውን መሰረታዊ ነገር እንዲያጡት የሚሆነው።

ሰዎች ከመሰል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አብሮነት ፣ ፍቅር ፣ መግባባት፣ መከባበር ፣ ህግ ፣ ስርዓት፣ ወንድማማችንነትን ከማስተማር ባለፈ በህግ ማረም ፣ ነገ መዘዙ የከፋ እየሆነ ስለሚሄድ ከወዲሁ እንዲገታ በአንድ ላይ ማውገዝ ፣ ተበዳይን መካስ ፣ እውነት ህግ የበላይ ነው የምንል ከሆነም ለራሳችን ስንል ህግን ሁሌም ማስከበር ነው።

ዛሬ ላይ እንዲህ ያሉና ከዚህ ቀደምም በየሀገሪቱ ክፍሎች የሰማናቸው ፍጹም አደገኛ የሚባሉ ጉዳዮች የሳምንት አጀንዳ እየሆኑ እያለፉ ይመስለን ይሆናል ግን በእርግጠኝነት መዘዛቸው የከፋ ሊሆን ይችላል።

ውጤታቸው ዛሬ ሳይሆን ውሎ አድሮ ምናልባትም አመታትን አልፎ ይታይ ይሆናል ስለሆነም እናስብበት ! ትውልዱን ከስህተቱ እናርመው ፤ ወገኑን እንዲጠላ ሳይሆን እንዲወድ ፣ እንዲያከብር እናስተምረው።

በሁሉም ዘንድ አውቀናል ታውቀናል ፣ ዛሬ ስልጣን አለን፣ ሚዲያውም የኛው ነው የምንል ሰዎችም ' አይ የኔ ወገን ስለሆነ ፍጹም ጻዲቅ ነው ፣ አይሳሳትም ፣ ጀግና ነው ፣ ቢሳሳትም ምንም ችግር የለውም እኔ እከላከልለታለሁ ' ከሚል አደገኛ እና ብዙ መዘዘ ካለው አመለካከት መራቅ ይገባናል።

#TikvahFamily
#Ethiopia

@tikvahethiopia
#ሴጅ_ማሠልጠኛ

10ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://hottg.com/sagetraininginstitute
Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute
Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች። እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች። ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።…
#Update

በኢራን " ኢስፋሃን ከተማ " ዛሬ ማለዳ ፍንዳታዎች የተሰምተው ነበር።

ይህች ከተማ የአገሪቱ አየር ኃይል መቀመጫ ፣ በርካታ ወታደራዊ ተቋማት ያሉባት ናት።

የኢራን መገናኛ ብዙኃን በደፈናው 3 ድሮኖች በኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓት ወድመዋል ሲሉ ገልጸዋል።

#የአሜሪካ ባለልስጣናት እስራኤል ቅዳሜ ለተፈጸመባት ጥቃት ኢራን ላይ የሚሳኤል የአጸፋ ጥቃት ፈጽማለች ብለዋል።

የኢራን በይፍ የሰጠችው ማብራሪያ ባይኖርም የተሰማው ፍንዳታ ጥቃትን የማክሸፍ እንደነበር አሁን ላይ ከተማዋ በመደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የደረሰ አንዳች ጉዳት እንደሌለ ጠቁመዋል።

በኑክሌር ተቋማት ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተነግሯል።

ምንም እንኳን በመገናኛ ብዙሃን እና በአሜሪካ ባለስልጣናት እስራኤል የጸፋ እርምጃ መውሰዷ ቢነገርም ሀገሪቱ እስካሁን በይፋ " ኃላፊነት እወስዳለሁ " አላለችም።

ኢራንም ፥ " እስራኤል ናት ይህንን ያደረገችው ቀጣይ እርምጃዬ ይሄ ነው " የሚል ይፋዊ ቃል አልሰጠችም።

ነገር ግን ጉዳዩ አሁንም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን እንደደቀነ ይገኛል።

ሀገራት ከወዲሁ በእስራኤል ላሉ ዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ናቸው።

ኢራን እስራኤልን ከቀናት በፊት መደብደቧን ተከትሎ እስራኤል የአፀፋ እርምጃ እንደማይቀርላት ተናግራለች።

ኢራንም እስራኤል የአጸፋ እርምጃ እወስዳለሁ ካለች እስከ ዛሬ ጥቅም ላይ ያልዋለ መሳሪያ እንደምትጠቀምና እርምጃዋ ከመጀመሪያው እየከፋ እንደሚሆን አስጠንቅቃለች።

ኢራን ፥ ጦርነቱ እንዲስፋፋ እንደማትፈልግ ነገር ግን ደፍሮ የሚያጠቃት የትኛውም አካል ካለ " እጁን እንቆርጥለታለን " ስትል ነው ከሰሞኑን የዛተችው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" የሟች ቤተሰብ ተገኝቷል " - ፖሊስ

በሟች ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ በማጣቱ  ምክንያት የሟችን ፎቶ በመለጠፍ  ቤተሰቦቹን አፋልጉኝ ያለው የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ የሟች ቤተሰብ መገኘቱ አስታውቋል።

የማህበራዊ የትስስር ገፆችና ሚድያዎች በሟች ቤተሰብ ፍለጋ ያደረጉት የነቃ ወገናዊ ተሳትፎና ጥረት አመስግኗል።

ለሟቹ ቤተሰብ ክብር ሲባል ፎቶውን ከገፃቸው በማጥፋት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።

በዚህም መሰረት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሟች ቤተሰብ ክብር የሟችን ፎቶ #ማጥፋቱን ለመላ አባላቱ መግለጽ ይወዳል።

ምናልባት በውስጥ የተቀባበላችሁም የሟችን ፎቶ ከስልካችሁ እንድታጠፉ እንጠይቃለን።

ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት በዓዲግራት ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተጥሎ መገኘቱንና በግድያው የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች ሟቹ ከወደቀበት አቅራቢያ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸው መረጃ እንደላክልንላችሁ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#BankofAbyssinia

በተለያዩ ቦታዎች በአፖሎ ሲከፍሉ ቅናሽ ያገኛሉ!

አሁኑኑ መተግበሪያውን በማውረድ ይጠቀሙ።

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የፋሲካ ኤክስፖ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የመግቢያ ትኬትዎን በቴሌብር *127# ወይም http://onelink.to/fpgu4m በመግዛት ጎራ ይበሉ፤ እስከ ብር 2500 ለሚደርሰው ግብይትዎ የአየር ሰዓት እና ጥቅል የሚገዙበት 10% ተመላሽ ያግኙ፡፡

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
" ልጄን አድኑልኝ " - መምህርቷ እናት

መምህርት አልሻምጌጥ ንጉስ ፤ ልጇ የአብቃል በተወለደ በሀያ አንድ ቀኑ ነው የልብ ህመም እንዳለበት ያወቀችው።

ላለፉት 5 አመታት የህጻናት የልብ ቀዶ ጥገና መዕከል አስመዝባ ብጠብቅም ወረፋ ሊደርሳት አልቻለም።

" አሁን ልጄ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደረሰ " ስትል ገልጻለች።

ከሀያ አንድ ቀኑ ጀምሮ ከሀዋሳ አዲስ አበባ እየተመላለሰች ሰርጀሪውን ስትጠብቅና ማስታገሻ መድሀኒት ስትጠቀም ብትቆይም እንደልጅነቱ መቦረቅ ያልቻለው የአብቃል  " አሁን ላይ የልቡ ክፍተት አራት ሚሊ በመድረሱ እብጠት ፈጥሮበታል " ስትል አስረድታችለ።

ይህ እብጠት ምግብ እንዳይረጋለት ከማድረጉ በላይ በአፍና በአፍንጫዉ ደም መውጣት መጀመሩ እና ድንገት በየሰአቱ እራሱን ከመሳቱ በተጨማሪ ፍጹም የድካም ስሜት ውስጥ እንዲገባ በማድረጉ ለቤተሰቡ ታላቅ ድንጋጤ ፈጥሯል።

ይህን ተከትሎ ጤና ባለሙያዎች በቶሎ ሰርጀሪዉ መሰራት እንዳለበት ቢናገሩም የመምህር ደሞዙን ከእለት ጉርስ አበቃቅቶ ለመድሀኒት ሲጠቀም ለቆዉ የመምህር አልሻምጌጥ ቤተሰብ ዱብ እዳ ሆኖበታል።

ቤተሰብም አሁን ላይ የሚያደርገዉ ጠፍቶበታል።

በጉዳዩ ላይ ለኢትዮጵያ ህዝብ በቲኪቫህ ኢትዮጵያ በኩል መልእክት አስተላልፉልኝ የምትለው እናት አሁን ላይ በግል ሆስፒታል ለሰርጀሪዉ ብቻ 650 ሽህ ብር እንደተጠየቀ በአጠቃላይ ከ800 እስከ 900  ሽህ ብር እንደሚያስፈልግ ገልጸለች።

ይህን ማድረግ ባለመቻሏ እና ገንዘብም ስለሌላት ልጇን አይኗ እያዬ ልታጣዉ መሆኑን በእንባ ተናግራለች።

በመሆኑም ፥ " ደጉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚቻለዉን አድርጎ ልጄን ያድንልኝ " በማለት ተማጸናለች።

መምህር አልሻምጌጥ ንጉስን በስልክ ማነጋገር የሚፈልግ የግል ስልክ ቁጥሯ 0916155490 ነው። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000243926053 የሂሳብ ቁጥሯ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
 #ትግራይ #መምህራን " ጥያቄያችን ፍትሃዊ ምላሽ ካላገኘ ወደ ቀጣይ እርምጃ እንገባለን " - የትግራይ መምህራን ማህበር የትግራይ መምህራን ማህበር ፤ ጥያቄያችን ፍትሃዊ መልስ ካላገኘ በምክር ቤት አስወስነን ለቀጣይ ትግል እንዘጋጃለን " አለ። የትግራይ መምህራን ማህበር ፤ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የ5 ወራት ውዙፍ ደመወዝ ለመክፈል የገባው ቃል እስከ አሁን አልተገበረም ብለዋል።  መምህራን ውዙፍ ደመወዝ…
" የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር ስለ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  - ማህበሩ

የትግራይ መምህራን ማህበር በድጋሚ የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል ጠየቀ።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርንም ዳግም አስጠነቅቋል። 

ማህበሩ ሚያዚያ 8 በኣክሱም ከተማ 33ኛው ጉባኤውን አካሂዶ ነበር። በጉባኤው ማጠቃለያ ባወጣው የአቋም መግለጫ " የትግራይ መምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛቸው እንዲከፈል " ሲል ጠይቋል።  

የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ እስከ ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከሚመለከታቸው የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር በመገናኘት ስለ ውዙፍ ደመወዝ መከፈል የመጨረሻ አቋሙ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል።

ለጥያቄው በጊዜ ገድብ የተወሰነ አሳማኝ መልስ ካላገኘ ጠበቃ አቁሞ ክስ እንደሚመሰርት አሳውቋል።

" ተቃውሟችን እና ጥያቄያችን ትምህርት ቤቶች በመዝጋትና ተተኪ ዜጋ በመጉዳት የማሳካት ፍላጎት የለንም " ያለው ማህበሩ " ግዴታችን እየፈፀምን መብታችን እስከ ጫፍ እንጠይቃለን " ብሏል።

" የመምህራን የስነ-ልቦና ቁስል ሳይሽር በትምህርት ስለሚገነባው ትውልድና የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ማሰብ ይከብዳል "  ሲልም አክሏል።

ማህበሩ የመምህራን ጥያቄ እስኪመለስ ህጋዊ ተቋውሞ ማሰማቱን እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

መረጃውን የመቐለው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ ድምጺ ወያነ ቴሌቪዥንን ዋቢ አድርጎ ነው የላከው።

ፎቶ ፦ ፋይል
      
@tikvahethiopia            
የከባድ መኪና ሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሹፌሮች በተለያዩ ወቅቶችና ቦታዎች በታጣቂዎች የሚደርስባቸውን ፦
- ግድያ ፣
- እገታ ፣
እምዲሁም የተሽከርካሪዎች ቃጠሎ በተመለከተ በተደጋጋሚ መረጃዎችን መለዋወጣችን ይታወሳል።

ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን መቂ አካባቢ “ የታጠቁ ኃይሎች ” በአሽከርካሪና ረዳት ላይ ጉዳት እንዳደደረሱ ፣ ከወራት በፊትም በርካታ ተሽከርከርካሪዎች ታቃጥለው እንደነበር ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ የመቂ ነዋሪ ፥ አንድ የአይሱዚ ሹፌር ሲገደል ፣ ረዳቱ አካላዊ ጉደት እንደረሰበትና ሌሎች ተሽከርካሪዎች በጥይት እንደተበሳሱ አስረድተዋል።

" የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸው ሹፌሩ ተገደለ። ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ነው የተቀበረው ፤ ረዳቱም ቆሰለ " ሲሉ ነው የተናገሩት።

የተኩስ እሩምታ የተከፈተባቸው ከ7 በላይ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ጠቁመው " ተዘግቦ እንኳን አየዋለሁ ብዬ ነበር የዘገበው ሚዲያ የለም " ብለዋል።

ሟቹ ሹፌር መነሻውን አዲስ አበባ በማድረግ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት መቂ አካባቢ ማታ ላይ በታጣቂዎች ተኩስ እንደተከፈተበት አስረድተዋል።

" ሌሎቹ ሹፌሮች ፈጣሪ አትርፏቸው አልተጎዱም። ተሽከርካሪዎቻቸው ግን በጥይት ተበሳስተዋል። ጎማው እስከ 15 ጥይት  ያረፈበት አለ " ብለዋል።
 
እኚሁ ነዋሪ ታጣቂዎች " ወደ ኦሮሚያ ተሽከርካሪ እንዳይሄድ ሰሞኑን እቀባ ጥለዋል " ያሉ ሲሆን ጥቃቱን በከፈቱ በማግስቱ  " ከመከላከያ ጋ ተታኩሰዋል "  ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላኛው ነዋሪ ፤ የዛሬ ወር ገደማ በተመሳሳይ እዛው ቦታ/መቂ ብዙ ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ሲሉ አስታውሰዋል።

" ጥቃቱ አለ አሁንም አልቆመም። የተወሰነ ጊዜ መከላከያ ሲመጣ ጋብ ይላል እንጂ። ሹፌሮች ስቃይ ላይ ናቸው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ እጅግ ትኩረት ይሻል የተባለውን የሹፌሮችን ጥቃት በተመለከተ ከክልሉም ሆነ ከዞኑ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ምላሽ የሚሰጡ ከሆነ የሚያስተናግዳቸው መሆኑን ያሳውቃል።

NB. መቂ ከሰሞኑን ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ግድያን ያስተናገደች ከተማ ናት።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኪርጊስታን ውስጥ እንዲታገድ ተወሰነ። ኪርጊስታን " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው በሚል ሙሉ በሙሉ እንዲታገድ ወስናለች። ውሳኔውን ያሳለፈው የሀገሪቱ የባህል ፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ነው። ሚኒስቴሩ ባደረገው ግምገማ መሰረት " ቲክቶክ " ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ መቆጣጠሪያ…
#Update

የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ።

ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል።

በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል።

ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው።

ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው።

የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን
- አእምሯዊ፣
- አካላዊ፣
- መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል።

በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል።

ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል።

መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው።

በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር።

ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር።

በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
HTML Embed Code:
2024/04/20 01:17:54
Back to Top