TG Telegram Group Link
Channel: FŰŇ_ŽØÑĘ 😂😱
Back to Bottom
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ

⚀ ክፍል አስራ አራት ⚀ 1⃣4⃣


🔅 ከእሷ በቀር በወጉ የሚረዳኝ ሰው እንደሌለ ውስጤ ያውቃል።
"ግሩሜ ፍሌም እኮ ነኝ ለምን የሆንከውን አትነግረኝም"አለችኝ ወደ አንገቷ ስር ጎትታ እያቀፈችኝ።
"የኔ ጌታ ከምልህ በላይ ናፍቀኸኛል። እየሸሸከኝ እንደሆነ ይሰማኛል። ግሩሜ እንደምታፈቅረኝ አልጠራጠርም። እኔ በጣም ነው የምወድህ። እኔ የማስበው ፍቅር ለመስጠት እንጂ ለመቀበል ቦታ እንደሌለው ነው። ለዚህም ነው አንተን አጥሮ ያገደኝን የስሜትህን ኬላ አፍርሼ የምወተውትህ። አንተን ስለማፍቀሬ እንጂ አንተ ለእኔ ስለምትሆንልኝ ነገር እየተነበይኩ ልረብሽህ አልሻም። ዛሬ ይህን ያህል ጊዜ ስንራራቅ ለምን አልፈለግከኝም ብዬ ማኩረፍ ነበረብኝ። ግን ማፍቀሬ ስለመስጠት እንጂ ስለመቀበል አላደላም።

ግሩሜ የኔ የፍቅር ስሌት
1+1 = 2 ሳይሆን 1+1= 1ነው።

ምክኒያቱም የኔ እና የአንተ ፍቅር ተደምሮ ሁለት የሚባል ፍቅርን አይሰጠንም። ግሩሜ መቀበልን ስታስብ ነው 1+1=2 የሚሆነው።
አንተ እንዲደመር መስጠት እንጂ ድምሩ ሁለት ሆኖ ካላየሁ ብለህ ግብግብ መግጠም የለብህም። አንድ ቀን ሳታስበው በውጤቱ ትደሰታለህ።"
አለችኝ ይህን ስትለኝ አልቻልኩም ሆድ ባሰኝ ከእቅፏ ውስጥ ተሸሽጌ ተንሰቀሰቅኩኝ። ገና ልነግራት የፈለግኩትን ነገር ቀድማ ትነግረኛለች። በግልፅነቷ ብቸኝነቴን ታሸሽብኛለች። ከሰው በቀደመ አድማስ ሰፊነቷ ጭንቀቴን ታባርልኛለች። ፍሌም የሰው ወርቅ! ሰው የመሆን ልክ!
ለፍሌም የሆንኩትን ሁሉ ፍርሃቴን ሳይቀር በግልፅ ምንም ሳልደብቅ ሁሉንም ነገር ነገርኳት ፍሌም ደስ አላት። ከቁዘማ አለሟ ወጥታ ተፍነከነከች።
ይሄ ደስታዋን እናቴ እንድታይ ተመኘሁ።"ፍሌሜ ለምን እናቴ ጋ ቤት ሄደን ትንሽ ተጫውተን አትሄጂም?" አልኳት የአፍንጫዋን ጫፍ በእጄ ጎተት ጎተት እያደረግኩ።
"እሺ እዛ ቤት ሁሉም ሰው ነው የናፈቀኝ። በተለይ የትርሃስ ንጭንጭ።" አለች "እሺ አላቆይሽም ቶሎ እሸኝሻለሁ" አልኳት።
"ፈቅደውልኝ እንኳን አብሬያችሁ ባደርኩ!"
"እ..ህ አጎትሽስ?" አልኳት
"ፊልድ ከወጣ ሁለት ሳምንቱ ነው። እኔ እና አንተ ከተጠፋፋን ጀምሮ እንደሄደ አልመጣም" አለች ቅር እያላት። "ብቻሽን ነበርሻ! ይህን ሁሉ ጊዜ?"አልኳት።
ታዲያ ምን ምርጫ አለኝ ደጋግሜ ቤት አንተጋ ብመጣ የለም ይሉኛል።መሄጃ ሲጠፋኝ ተኝቼ እውላለሁ!" አለች ትክዝ እንዳለች።

ክፍል አስራ አምስት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @ABDSEwAnTED


"SHARE" @ONLYZEGET
እሷ ወዳኝ እኔ እንድጀነጅናት ከምትፈልግ ቸከስ በላይ ጁንታ የለም🤨
GM
@Abdsewanted
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.
⚀ ክፍል አስራ አምስት ⚀ 1⃣5⃣




"ብቻሽን ነበርሻ! ይህን ሁሉ ጊዜ?..."አልኳት።
" ታዲያ ምን ምርጫ አለኝ ደጋግሜ ቤት አንተጋ ብመጣ የለም ይሉኛል። መሄጃ ሲጠፋኝ ተኝቼ እውላለሁ!" አለች ትክዝ እንዳለች።
በነገረችኝ ነገር በእራሴ አዘንኩ የራሴን ስሜት እየሰማሁ ለካስ ፍሌሜን ጎድቻታለሁ ብዬ ተፀፀትኩ። ግን ፍሌም ይህን ያህል አድርጌያትም አልተለወጠችብኝም።
ምንም በልቧ የለም። ንፁህ ነች። ልቧን አደነቅኩላት ፤ ይበልጥ ስወዳት ተሰማኝ።
ይህቺ ፍካት ህይወቴን አጥርታ እኔነቴን አፈካችው። ልቤ ወገግ ሲል ይሰማኛል።
ፍሌም የሰው ወርቅ!
በድብስብስ ቀን ያገኘዋት ፀሀይ በድብስብስ አለም የታደልኳት ጎህ ፍሌም።
የብቻዬ ነች ብዬ ለልቤ ነገርኩት።
ሰማይና ምድሬ ነች።
ቀኑ ደንገዝገዝ እያለ ነበር በአዌቱ ውሃ እንደ ህፃን ልጅ ፊቷን አጥቤ ወደቤት ወሰድኳት።
................. #########..................
እንደዋዛ ትምህርት ተጀምሮ መንፈቅ አመት ሊሆነው ምንም አልቀረም። እኔና ፍሌም ያለውን ነገር ተነጋግረን እዚህ ለመማር ከወሰነች ወዲህ መንቲና በሚገኘው የጅማ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት እሷ 11ኛ እኔ የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪ ሆነን እየተማርን ነው።
ዘውትር ተሳስበን እና ተዋደን ነው የምንኖረው። ትምህርት ቤት ስንሄድም ሆነ ስንመጣ አብረን ነን ተነጣጥለን አናውቅም።
እሁድ እሁድ ሁሌም ማምሻውን በጀምበር መጥለቂያ ደርብ ላይ ወጥተን ጀምበርን እያጠለቅን እናወጋለን።
በየካፌውና ሬስቶራንቶች ላይ እየተዟዟርን በትምህርት በኑሮ የተጨናነቀ መንፈሳችንን እናድሳለን። እኔም ሆንኩኝ ፍሌም በእጅጉ ደስተኞች ነን።
ትርሃስ ዘንድሮ የ10 ክፍል የሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ስለሆነች ከእኔም ሆነ ከፍሌም ጋር የመገናኘታችን እድል የጠበበ ነበር።



ክፍል አስራ ስድስት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @abdsewanted


"SHARE" @onlyzeget
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.
⚀ ክፍል አስራ ስድስት⚀ 1⃣6⃣


.
ትርሃስ ዘንድሮ የ10 ክፍል የሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ስለሆነች ከእኔም ሆነ ከፍሌም ጋር የመገናኘታችን እድል የጠበበ ነበር።
አንድ ቅዳሜ ጠዋት ህይወታችንን ያመሰቃቀለ ነገር ተፈጠረ።
ቀኑ ቅዳሜ ጠዋት ነበር። እስከ አምስት ሰዓት ተምረን ቤት ስገባ ቤቱ ጭር ብሏል። እየተጣራው ገባሁ። ቤት ስገባ ደስ ብሎኝ ነበር የገባሁት እኔና ፍሌም የሁለተኛ መንፈቅ አመት ከጀመሩ በፊት ባለችው የእረፍት ጊዜ ድሬ እንደምትወስደኝ እና ከእናት አባቷ ጋር እንደምታስተዋውቀኝ ከክፍል ስወጣ ነግራኝ ነበር።
ደስ ብሏታል። ስለእኔም ብዙ ነገር እንደነገረቻቸው ጨምራ አውግታኛለች።
ፍትት ብዬ እናቴን እየጠራዋት ኩሽና ስገባ እናቴ ሽንኩርት እየላጠች ነበር።
" እማ እንዴት ዋልሽ?" አልኳት ጉንጯን አጥብቄ እየሳምኩ።
" እንዴት ዋልክ ጌቱ!" ብላ በተራዋ ግንባሬን ሳመችኝ። (ጌታዬ ጌቱ የኔ ጌታ እያለች ነው የምትጠራኝ።) የኤሌክትሪክ ምድጃውን ለኩሳ ውሃ እስክትጥድ ሽንኩርቱን እከትፍላት ጀመር።
"እማ! ሚሚዬ የት ነች ?" አልኳት ሽንኩርቱ እያቃጠለኝ ከአይኔ የሚወጣውን እምባ በአይበሉባዬ እየጠረግኩ።
"መቼ ከትምህር ቤት መጣች ብለህ ነው ጌታዬ!?" አለች። ለወጥ የሚሆን ቲማቲም እየመረጠች።
"ናፈቀችኝ እኮ እማ ! አይ ትርሃሴ" አልኳት
"ምን ጭቅጭቋ ነው የሚናፍቅህ አይ እናንተ! እንደው ጌታዬ እናንተ ባትኖሩ ምን እሆን ነበር ቸሩ መድሃኒያለም ጥሎ አልጣለኝም ቤቴን በፌሽታ ሞላችሁት እኮ!" አለች በእናታዊ የመንሰፍሰፍ ሀዘኔታ ባለው ድምፅ ቲማቲሙን አምጥታ ከፊት ለፊቴ እያስቀመጠች።
"እማ ዛሬ ደስ ብሎኛል የሆነ የምነግርሽ ነገር አለኝ። አንቺም ደስ እንደሚልሽ አልጠራጠርም!" አልኳት።
"አድርጎት ነው የኔ ጌታ አንተ ብቻ ደስተኛ ሁንልኝ እንጂ ደስ ያለህ ነገር እኔንም ደስ ያሰኘኛል።"ብላ መጥታ በስስት ጉንጬን ሳመችኝ።
ስልኬ ላይ የሆነ ነገር ላሳያት ብዬ ስልኬ እኔ ጋ እንዳልሆነ ኪሴን ዳብሼ ስረዳ ከደብተሬ ጋር ሳሎን እንደተውኩት ገባኝና እናቴን "መጣው እማ!" ብዬያት ወደ ሳሎን አቀናው።
ስልኬን ይዤ ልመጣ ስል ባትሪ ዘግቶል። ከቻርጀር ጋር ኩሽና ሰክቼ ከእናቴ ጋር ማውራቴን ቀጠልኩ።
"እማ ምነው ትርሃሴ ቆየች!? " አልኳት ቻርጀሩ መቀበል አለመቀበሉን እያረጋገጥኩ።


ክፍል አስራ ሰባት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @Abdsewanted

መልካም ቀን

"SHARE" @ONLYZEGET
🛑 እነዚህን 3 ነገሮች ሁሌም አስባቸው

1. አላማ ይኑርህ አለበለዚያ ጊዜው ሲገፋ በዘፈቀደ የሚኖር ከንቱ ሰው እንደሆንክ ማሰብህ አይቀርም፤

2. ወደ አላማህ አንድ እርምጃም ቢሆን የሚያስጠጋህን ነገር በየቀኑ አድርግ፤

3. በፈጣሪህ ታመን ከዛ ልበሙሉነት ፀባይህ ይሆናል ግን ሲሳካልህ አመስጋኝ እንጂ ጀብደኛ አትሁን!

ግሩም ቀን ተመኘንላችሁ
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.

⚀ ክፍል አስራ ሰባት⚀ 1⃣7⃣




እማ ምነው ትርሃሴ ቆየች!? " አልኳት ቻርጀሩ መቀበል አለመቀበሉን እያረጋገጥኩ።
"አሁን ትመጣልህ የለ!" ብላኝ ሳትጨርስ
"እማ እንዴት ነሽልኝ እናቴ !" እያለች ገባች። ከመቅበጥበጧ የተነሳ የምትዘፍን ነበር የምትመስለው።
"ሚሚዬ እንዴት ዋልሽ ልጄ?"
"አለውልሽ ኡፍፍፍ ደክሞኛል እማ ውሃ ስጪኝ በማሪያም?"
"እሺ እሺ ወንድምሽን ሰላም አትዪውም እንዴ? ምነው ትርሃሴ?" አለች
ባክሽ እኔ የማንንም ሽንኩርታም ሰላም ስል ጊዜዬን አላቃጥልም! You know time is the gold"አለች በጎሪጥ እየተመለከተችኝ።
"ማንን ነው አንቺ? አይጥ!"አልኳት ኮስተር ለማለት እየታገልኩ።
"እኔ ግሩም ብዬ ጠርቼሃለው ሽንኩርታም!" አለች ጀነን እንዳለች።
ሚሚዬ እግዚአብሔርን ይሄን ሽንኩርት አበላሻለሁ! ጥጋብሽን ቀንሺ "አልኳት።
"ወንድ ነኻ ዝም ስልህ የፈራሁህ መሰለህ? አመዳም! ግምባራም! ሂሽ ሽንኩርታም!!" አለች።
ከምከትፈው ሽንኩርት ላይ በእጄ ዘግኜ ወስጄ ላበላት ታስታገል ጮኸች።
"ግሩሜ በእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ግሩሜ የኔ ወንድም በእግዚአብሔር አዪዪዪ እማ ተው በይው እንጂ ኧረ በማሪያም እማ?!" አለች እየታገለችኝ
"አንቺ ማን ነገር ፈልጊው አለሽ እና ነው?" አለች እናቴ
"ኧረ እማ አበላኝ እኮ በእግዚአብሔር ቱ ምን አይነት ገገማ ነው በእግዚአብሔር " አለች ፊቷን ጭፍግግ አድርጋ ያበላዋትን ሽንኩርት እየተፋች
"አሁንም እንዳላበላሽ ዋ!"
"ሂድ ወደዛ ሽንኩርታም! ወንድ ነህ ግሩሜ አሁንማ"አለች ወደ እናቴ እየርጠች። እናቴን መሃል አድርገን ተያየን።
"ምነው ጌታዬ ብትተዉ ሽንኩርቱንም በትናችሁ ጨረሳችሁት እኮ አዬ ልጅነት"አለች ወደ እኔ ዞራ።
"አንቺም እረፊ ተሞጣሙጠሽ ስታበቂ እኔን አትጥሪኝ ደቃቃ" አለቻት በፍቅር ቁጣ
"እማ ግን ሁል ጊዜ እኔ ላይ ነው አይደል የምትጮሂው? እንዴ......" ትርሃስ እየተነጫነጨች ስልኬ ጮኸ።አነሳሁት።
"አቤት ፍሌሜ!" አልኩኝ
ከወዲያኛው የስልኩ ጫፍ
"ግሩሜ በፍጥነት ቤት ና እፈልግሃለው " የሚል የፍሌሜን ድምፅ እንደሰማው ስልኩ ተዘጋ።
ግራ ገባኝ ተነስቼ ከነፍኩ።
የትርሃስ ስድብና ንጭንጭ እስክወጣ እየተከተለኝ ነበር።


ክፍል አስራ ስምንት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @ABDSEWANTED

አንብባችሁ ሼር አድርጉት!!

"SHARE" @ONLYZEGET
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.
⚀ ክፍል አስራ ስምንት ⚀ 1⃣8⃣
.
ከወዲያኛው የስልኩ ጫፍ
"ግሩሜ በፍጥነት ቤት ና እፈልግሃለው " የሚል የፍሌሜን ድምፅ እንደሰማው ስልኩ ተዘጋ።
ግራ ገባኝ ተነስቼ ከነፍኩ።
የትርሃስ ስድብና ንጭንጭ እስክወጣ እየተከተለኝ ነበር።
➲➲➲➲➲➲➲➲➲➲➲
አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተንጋልያለሁ ትርሃስ አልጋው ጫፍ ላይ ሆና ታፋዋ ላይ አስተኝታኝ ጣቶቿን በፀጉሬ ውስጥ ታርመሰምሳለች። ፍዝዝ ብላለች ትክዝ ብያለሁ
"ግሩሜ " አለች ቅዝቅዝ ባለ ድምፀት
ዝም አልኩ!
"ለምን እንዲህ ትሆናለህ የኔ ጌታ! እራስህን እየጎዳህ እኮ ነው ግሩሜ ቢያንስ እናታችንን አስባት እስኪ ምን ያህል እንደተጎሳቆለች። ፈተናህም አንድ ወር ነው የቀረው። በዛ ላይ ፍሌም ከሄደች ይኸው ድፍግ አምስት ወር ሆናት አይደል እንዴ!" አባታችንስ ከታሰረ ሶስት ወር ሆነው አይደል? እሷስ ብትሆን የእውነት ከወደደችህ እና ካፈቀረችህ እንዴት ይህን ያህል ጊዜ ትተውሃለች?!" አለችኝ። እምባ በአይኗ እየቀረረ ሳግ እየተናነቃት።
ትመጣለች! እናቷ ሞተው ታዲያ በዚህ ፍጥነት .....እምባ አነቀኝ።እልህ ጉሮሮዬን ፈጥርቆ ያዘው።ትኩስ እምባዬ ጉንጬን እንደሳማ እየለበለበኝ እርግፍ እርግፍ ሲል ይታወቀኛል።
ፍሌም ናፈቀችኝ በዛች የተረገመች ቀን ጠርታኝ እናቷ እንደደከሙ እና አሁኑኑ መሄድ እንዳለባት እየተርበተበተች የነገረችኝ ነገር ሁኔታው በአይነ ህሊናዬ ውልብ አለ።
ከሄደች ጀምሮ በሽተኛ ሆኛለሁ። አልጋ ላይ ሆኜ እምባዬ አለከልካይ በጉንጮቼ ሲንፎለፎል ትርሃስ ጭንቅላቴን ወርውራ ተነሳች።
"ቆይ አንተ ምንድነው ፍላጎትህ.."እኔ አላሳዝንህም ? እማዬ አታሳዝንህም ? ቅዱሴን እንኳን ተመልከተው ግሩሜ! እኔ እህትህ እኮ ደስታህን እፈልገዋለሁ ቆይ ከፍትህ አልጋ ላይ ስትውል የማይከፋኝ ይመስልሃል ? ምን ስሆን ማየት ነው የምትፈልገው?.."
"ምንድነው ምን ሆናችሁ ሚሚዬ "እናቴ ከውጭ ገባች።
እማ እኔ ግሩሜ በዚሁ እየቀጠለ የሚኖር ከሆነ ከእኔም ሆነ ከቅዱሴ ምንም ነገር አትጠብቂ እንደውም እኔ እህቱ አይደለሁም! እማ ተመልከቺው እስኪ ምግብ በስርዓቱ የበላው መች ነው? ይሄን ልብስ ከቀየረው ስንት ጊዜው ነው? እኔና አንቺን መች አይቶን ያውቃል? የታሰረ አባቱን ከጠየቀው ስንት ጊዜ ነው? እማ በእግዚአብሔር ጠይቂው ጨነቀኝ እንደድሮ አያናድደኝም ስድቤ አይናፍቀውም እማ የድሮው ግሩም ናፈቀኝ... !" ብላ ልትቀጥል ስትል እምባ ተናነቃት። አምቃ የያዘቸውን ለቅሶ አፈነዳችው። እየተንሰቀሰቀች ወጥታ ሄደች.....


ክፍል አስራ ዘጠኝ ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @ABDSEWANTED


"SHARE" @ONLYZEGAeT
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙

⚀ ክፍል አስራ ዘጠኝ ⚀ 1⃣9⃣

.
.... ብላ ልትቀጥል ስትል እምባ ተናነቃት። አምቃ የያዘቸውን ለቅሶ አፈነዳችው። እየተንሰቀሰቀች ወጥታ ሄደች....
እናቴ ግራ ገባት። ልትቆጣኝ አልወደደችም። እንድደነግጥ አልፈለገችም።
"የእኔ ጌታ ትንሽ ምግብ አትበላም?"አለች አይኗን ቡዝዝ አድርጋ እየተመለከተችኝ። በግምባሯ ላይ የተጋደሙትን እጥፋቶች ስመለከት በትልልቅ ችግር ውስጥ አላሳልፍ ብሎ የተጋደመ ትልቅ ግንድ ያየው መሰለኝ።
በረጅሙ ተንፍሼ እመባዬን እያበስኩ "በቃኝ እማ!" አልኳት።
"ግሩም ልጄ ምነው አሳቀቅከን ምነው ስቃዬን በቃሽ ብትለኝ ?
እህትህንም ሰላም አልሰጣሃትም! ተሰቃየች እኮ ጌታዬ እኔስ ባማጥኩህ በወለድኩህ ልጎዳ እህትን ምነው ልጄ!?
የኔ ጌታ ፈተናህን ተወው ይቅር ግን አንዴ ብቻ ተጣጥበህ ልብስህን ለውጠህ ምግብ ብላልኝ! ልጄ ባጠባውህ ጡት ይዤሃለው እባክህ እባክህ!" አለች እናቴ እምባዋን እያዘራች።
የለበሰችው ቢጃማ በላይዋ ላይ አድፏል። ስለእኔ ማሰቡ ክስት አድርጓታል። የድሮ ወዟን አጥታ አመዷ ቡን ብሏል። ይባስ ብሎ አባቴ ከሶስት ወራት በፊት ለአንድ ወር ከወጣበት የመስክ ስራ ሲመለስ ሰርቦ በተባለች የጅማ አዋሳኝ ትንሽዬ ከተማ ውስጥ ህፃን ልጅ ገጭቶ ከታሰረ ወዲህ እናቴ እንቅልፍ የላትም ትርሃሴም እንደቆዘመች ትውላለች። ታድራለች። በቤታችን ሰማይ ስር መከራ ጥቁር ጥላውን አጥልቷብናል።
ይሄን ፈተና ተፈትኖ ፍሌሜን ድሬዳዋ ሄጄ ልፈልጋት አሰብኩኝ። ትርሃሴን እና እናቴን ደስ እንዲላቸው ጠዋት ወጥቼ ማታ እገባለሁ።
ሀደኮ መጥታ ታየኛለች ብቻዬን ስታየኝ ውሃውን ሳትቀዳ ተመልሳ ትገባለች። ከፍሌም ጋር ፀሀይን የምናጠልቅበት ከጀምበር መጥለቂያ ላይ አንዳንዴ እሄዳለሁ ግን ምን ያደርጋል። ትዝታ ብቻ። ህይወት ለዛዋ ጠፍቶ ቀለም አልባ ትሆንብኛለች።
የጎዳናው ዳር ፣ የሲኒማው ቤት ፣ የመናፈሻ እና የሬስቶራንቶች ደስታው እና ፌሽታው ልጆችዋን እንደተራበች ወፍ በረው ጠፍተዋል።

....... .......

እንደምንም አንድ ወሬን ባጅቼ ፈተናዬን አጠናቅቄ ወደ ድሬዳዋ ለመሄድ ተነሳሁ። ትርሃሴ አብሬህ ካልሄድኩ ብላ አስጨነቀችኝ በስንት ውትወታ አስቀረዋት። ከሶስት ቀናት በኃላ " የበረሃዋ ንግስት " ወደምትሰኘው ታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ድሬ ከተማ ገባሁ።
ድሬ እውነተኛ ፍቅር እና መቻቻል የሚንፀባረቅባት ውብ ከተማ ነች። ሀገሬው ጭንቅ አይወድም። ጭንቀትም በአየሯ ላይ ቦታ የለውም በፈገግታና ፍቅር እየተባረረ ድንበሯን ጥሶ ይጠፋል።
ገና ከተማዋ ስገባ መንፈሱ የደስ ደስ ይሰጠኝ ጀምሯል።
ድሬ ፍቅር ፍቅር ትሸታለች።......


ክፍል ሀያ ይቀጥላል........

ደራሲ Cራክ
comment ፦ @abdsewanted

መልካም ምሽት እንደተለመደው አንብባችሁ ሼር አድርጉት!


"SHARE" @onlyzeget
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙

⚀ ክፍል ሀያ ⚀ 2⃣0⃣


.
ድሬ እውነተኛ ፍቅር እና መቻቻል የሚንፀባረቅባት ውብ ከተማ ነች። ሀገሬው ጭንቅ አይወድም። ጭንቀትም በአየሯ ላይ ቦታ የለውም በፈገግታና ፍቅር እየተባረረ ድንበሯን ጥሶ ይጠፋል።
ገና ከተማዋ ስገባ መንፈሱ የደስ ደስ ይሰጠኝ ጀምሯል።
ድሬ ፍቅር ፍቅር ትሸታለች።
.
ሁለት ሳምንታት ድሬን ዞርኩ ምንም ጠብ ያለ ነገር አላገኘውም። ወደ ጅማ መመለስ አልፈለግኩም።
ፍሌሜን አየዋት የሚለኝ ሰው አጣው።
ጀማ ሆኜ ሳስብ እንዲህም ተንከራትቼ የማጣት አልመሰለኝም ነበር። የበላት ጅብ አልጮህ ቢል ልቤ ቀቢፀ ተስፋውን ወደ መጥራቱ እያዘነበለ በነበረበት ሰሞን የሆነ ባለሱቅ ጋር ስለፍሌም ና ስለእኔ በደንብ አወጋን እሱም አሰብ አድርጎ ፍሌምን እንደሚያውቃት ነገር ግን ከቅርብ ወራት በፊት በድንገተኛ የመኪና አደጋ እንደሞተች እና እናትየው በህይወት እንዳሉ ነገረኝ።
ይህን ሲለኝ ሰማይ የተደፋብኝ ያህል ዞረብኝ የሰማውት ነገር ቅዠት እንጂ እውነት አልመስልህ አለኝ።
ግራ በተጋባ ስሜት ውስጥ ሆኜ ራሴን ጠላውት። ዛሬውኑ ድሬን ለቅቄ ለመሄድ ወሰንኩ። ግን ከዚህ ወዲህ ፍሌምን አጥቶ እንዴት ይኖራል? ዋ!!!
ግን ይሄ ሁላ እንዴት ሊሆን ቻለ?
ፍሌም እናቷ ካልሞቱ እንዴት ደክመዋል ተብሎ ሲቀጥልም ሞተዋል ብለው ጠሯት? ' እያልኩ ስብሰከሰክ ድሬ ከገባሁ ወዲህ የተዋወቅኩት አንድ ጫታም እየተንከወከወ መጥቶ የሆነ ሽማግሌ ጋ ወሰደኝ።
ሽማግሌው ወንድምየው ታሞበት እያስታመመ መሆኑን እና እውነተኛዋ እኔ የምፈልጋት ፍሌም እዚሁ ጊቢው ውስጥ እንዳለች ነግሮኝ ፍሌሜን ሊያሳየኝ ወደ ጊቢው ይዞኝ ገባ።
ፍሌም አለች የተባለችበት ሰርቢስ ውስጥ ነበር።
ስገባ ቤቱ ጭልምልም ብሏል። እሷን የሚመስሉ አሮጊት ሴትዮ ወደ አልጋው ትራስጌ ቆመዋል።
አልጋው ላይ ፍሌም ተኝታለች። ቀረብ ብዬ ተመለከትኳት።መልኳ ገርጥቷል።ፍሌሜን አሟታል፤,የድሮ መልኳ ተለውጧል።
ገና ስታየኝ እያቃሰተች ተጣጥራ አቀፈችኝ ፤ እምባዋን አዘራች።
አምርሬ አለቀስኩ ከፈጣሪዬም ጋር ተዋቀስኩ። በእጅጉ አለም እንደከዳችኝ ገባኝ።
ሳለቅስ ሽማግሌው የታመመ ወንድምየው እንዳይረበሽ ለቅሶዬን አስቁሞ ያፅናናኝ ገባ።
የማየው ነገር ሁሉ እውነት አልመስልህ አለኝ።
.... እንደዋዛ ከፍሌም ጋር ለሶስት ቀናት ቆየው። ከሚያስታምሟት እናቷ ጋር ሆነን የማይገፉ ሶስት ቀናትን የዘላለም ያህል እየከበደኝ ገፋሁት።
ፍሌሜም እኔ ፊት ደስተኛ ሆና ለመታየት ፈገግ ትላለች። ያ ውብ ዲንፕሏ ድምቀቱ ጠፍቶ የበርባሮስ ጉድጓድ መስሏል።



ክፍል ሀያ አንድ ነገ ምሽት በዚህ ሰዓት ይቀጥላል........

ምን ያህሎቻችሁ ፍሌምን ወዳችኋታል?
ደራሲ Cራክ
comment ፦ @Abdsewanted



"SHARE" @onlyzeget
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙

⚀ ክፍል ሀያ አንድ ⚀ 2⃣1⃣


.
ፍሌሜም እኔ ፊት ደስተኛ ሆና ለመታየት ፈገግ ትላለች። ያ ውብ ዲንፕሏ ድምቀቱ ጠፍቶ የበርባሮስ ጉድጓድ መስሏል።
ሽማግሌው የፍሄሜን የመዳን ጉጉት በእኔ ውስጥ አሻግሮ ከተመለከተ በኃላ ሊያድናት የሚችል የባህል መድሃኒት እንዳለና ሁለት ሳምንታት እንደሚፈጅ ነገረኝ።ሌላ ሰው ልከው እንዳልተመለሰ ሲነግሩኝ አላመነታሁም።ይህን ዜና በሰማው ማግስት ሰማይና ምድር ተራክቧቸውን አጠናቀው ሲለያዩ ማልጄ ጉዞ ጀመርኩ።
.... የአስር ቀናት ጉዞን ተጉዤ በሀረር አቅጣጫ ወደ ገጠሩ ዘልቄ የተባለውን መድሃኒት ይዤ ግመሌን እየጎተትኩ 18 ቀን ከፈጀ አድካሚና አሰልቺ ጉዞ በኃላ ድሬ ገባሁ።
የእለቱ ፀሀይ ሀሩር ነበር። ረጫሞው እንደጉድ ይፋጃል። ፍሌሜ ወዳለችበት መንደር ስቃረብ ደነገጥኩ ሀሞቴ ፍስስ አለ ብዙ ሰው ጭንቅላቱን ይዞ እያለቀሰ ፍሌም ወዳለችበት ጊቢ ይገባል ይወጣል። ይህን ሳይ እግሬ ቄጤማ ሆነ። ሆዴ ክፉኛ ተሸበረ ውስጡ የነበረው የመኖር ተስፋ እየተሟጠጠ ቀፎ ሲሆን ይሰማኛል።
ከግመሏ ጀርባ ላይ ገመድ ፈትቼ ወደ ኃላ ወደ በረሃው ሸሸው።
ከለቀስተኞች ውስጥ ስመለስ አይቶ የተከተለኝ ስለመሰለኝ ረጅም መንገድ ሮጥኩ።
ከዚያ ዙሪያ ገባውን ቃኘውት። በረሃ ነው አንድም ዛፍ የለም።
አንድ ሀሳብ መጣልኝ ከርቀት የባቡር ጣቢያ ቤት ነገር አየው። መቆጣጠሪያው ነው ብዬ ገመትኩ።
ወደ እግሬ ተመለከትኩ የቆምኩት የባቡር ሀዲድ ላይ ነው።
ላቡ እንደ ጅረት በክንድ እና ክንዷቼ ላይ እየተንቆረቆረ ውሃ ወደ ማይጠግበው የበረሃው አሸዋ ላይ ይንጠፈጠፋል።
ቀና ብዬ ፀሀይዋን አየዋት በአናቴ ትክክል ናት። አሁን የከሰዓቱ ባቡር ከተለያየ አቅጣጫ ድሬ የሚገባበት ሰዓት ነው።
ጆሮዬን ከሀዲዱ ጋር አጣብቄ አዳመጥኩ ግምቴ ልክ ነበር ። ድምፅ ሰማው።
ቶሎ ብዬ ሀዲዱ ላይ ተቀምጬ እራሴን ከሀዲዱ ጋር መተብተብ ፣ መጠፈር ያዝኩ። ቀድሜ ሁለቱ እግሮቼን ከሀዲዱ ጋር ጠፍሬ አሰርኩት። ቀጥዬ እጅና እጆቼን አጠላልፌ አሰርኳቸው።
ከዚያ ባቡሩን መጠበቅ ጀመርኩ። ፍሌሜን አጥቼ መኖር ስለማልችል ፣ እሷ ሞታ በመቃብሯ ላይ ቆሜ እህህ እያሉ ቀን መግፋት ስለማይሆንልኝ ባቡሩ ድጦኝ እንዲያልፍ ፈቅጃለሁ።
ባቡሩ ቢቀርበኝና ህይወት አሳስታኝ ልትረፍ ብል እንኳን እራሴን ሆነ ብዬ ከሀዲዱ ጋር ተብትቤዋለሁ ለመፍታትም ባቡሩ ጊዜ አይሰጠኝም።
የባቡሩን ሀዲድ እና ትብታቡን አንቼ ቀና ስል.....
........ .......


🛎 የመጨረሻው ክፍል ነገ ምሽት ይቀጥላል......
ፍሌም...

➲ ደራሲ Cራክ
➲comment ፦ @abdsewanted
Creator ፦



"SHARE" @onlyzeget
⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙

⚀ የመጨረሻው ክፍል ⚀


.....ጆሮዬን ከሀዲዱ ጋር አጣብቄ አዳመጥኩ ግምቴ ልክ ነበር ። ድምፅ ሰማው።
ቶሎ ብዬ ሀዲዱ ላይ ተቀምጬ እራሴን ከሀዲዱ ጋር መተብተብ ፣ መጠፈር ያዝኩ። ቀድሜ ሁለቱ እግሮቼን ከሀዲዱ ጋር ጠፍሬ አሰርኩት። ቀጥዬ እጅና እጆቼን አጠላልፌ አሰርኳቸው።
ከዚያ ባቡሩን መጠበቅ ጀመርኩ። ፍሌሜን አጥቼ መኖር ስለማልችል ፣ እሷ ሞታ በመቃብሯ ላይ ቆሜ እህህ እያሉ ቀን መግፋት ስለማይሆንልኝ ባቡሩ ድጦኝ እንዲያልፍ ፈቅጃለሁ።
ባቡሩ ቢቀርበኝና ህይወት አሳስታኝ ልትረፍ ብል እንኳን እራሴን ሆነ ብዬ ከሀዲዱ ጋር ተብትቤዋለሁ ለመፍታትም ባቡሩ ጊዜ አይሰጠኝም።
የባቡሩን ሀዲድ እና ትብታቡን አንቼ ቀና ስል.....
.
ባቡሩ እየገሰገሰ ወደእኔ እየመጣ ነው።ግፋ ቢል ሁለት ደቂቃ ቢቀረው ነው።
የአሸዋውን አቧራ እያቦነነ መጣ። ልቤ ተሰቀለች። መሞት ፈራው። ልቤ ቶሎ ቶሎ ትመታ ጀመር።
እናቴን አሰብኳት ፣ የታሰረ አባቴን አሰብኩት፣ፍሌሜን አሰብኳ ፣ ትርሃሴን አሰብኳት.....ቀና ስል...አንዲት ልጃገረድ ቢጤ እየሮጠች ወደ እኔ ስትመጣ ተመለከትኩ።
በደንብ ስትቀርብ ሳያት ለየዋት። ፍሌም ነች።ባቡሩን አየውት በጣም እየቀረበኝ ነው። መልዓከ ሞትን አስቀድሞ የሚገሰግስ የሞት ሰራዊት መሰለኝ ።
ፍሌም ሻርቧን ነፋሱ ነጥቋት ሲሄድ እያየው ወደ እኔ እየሮጠች " ግሩም..! ግሩም..!" አለች።....ባቡሩ ፈጠነ።
እኔም የታሰርኩበትን ትብታብ በደመ ነፍስ መፈታታት ጀመርኩ።
ባቡሩ ቀ.....ረ......በ... በፍጥነት የእጄን ትብታብ ፈትቼ ወደ እግሬ ገባሁ። አንዱ እግሬን ፈትቼ ስጨርስ ቀግምት 8 ወይም 7 ደቂቃ ያህል ቢቀረው ነው።
ፍሌሜ በደረቷ አሸዋው ላይ እራሷን ስታ ወድቃለች።
ትብታቡን ለመፈታታት እታገላለሁ። ባቡሩ ሊድጠኝ ይገሰግሳል..........


❂───── ❁ ተ ፈ ፀ መ ❁ ───── ❂

➲ ደራሲ Cራክ
➲comment ፦ @aBdSEwAnTeD


ስለተከታተላችሁን እናመሠግናለን በቀጣይ በሌሎች ስራዎች ዳግም እንገናኛለን!!🙏

ስራችንን ወዳችሁታል? ❤️

"SHARE" @onlyzeget
እኩዮቼ በኮንቴነር ዕቃ አስጭነው " ጅቡቲ ደረሠ ? ዱከም ደረሠ ? " ይላሉ እኔ እዚህ ቁጭ ብዬ " ላይኬ ስንት ደረሠ ? " እያልኩ ስቆጥር እውላለሁ😜🤣
አንዱ በግ ሊገዛ ሔዶ 7000 ብር ሲሉት...

ምነው እረኛዬ ላይ ሰርታለች እንዴ🤣🤣
ቆይ ግን ምን አይነቷ ልጅ ነሽ? እኔኮ
በጣም እዎድሽና እጨናቅልሽ ነበር ግን
እንደዚ አይነት ልጅ ነሽ ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር በቃ በጣም ነው የስጠላሺኝ ቆይ ግን አይደብርሽም
ሁሉም ጋር እየ ሄድሽ ስላኔ ዝም ብላሽ ማያገባሺን ምት በጣርቂው በጥራቃ!! በቃ ይገባሽ ከ ሆነ ከዛሬ ቧላ የኔን ስም እንዳታነሺው ባቃ እርሺኝ እኔ ከዛሬ ብዋላ እንደ ሌላው እይኝ

ብሎሀል 2013 hhhh መልካም አዲስ አመት



@ABDSEWANTED
ሴት ከሆንሽ አንዴ ስሚኝ 👂👂

ወንዶች ሁላ አንድ ናቸው
የማለት መብት የለሽም
የምሬነው ምልሽ እንደዚች አይነት ሴት ከሆንሽ
እንደዚህ የማለት መብት የለሽም!
ከሁሉም ጋር online እያወራሽ ከዚም ከዚያም
ሰዓት እላፊ እያወራሽ ትኩረትሽን ሰተሽ
በተለይ
telegram ላይ 100 ምናምን ጥያቄ ልኮ ትእዛዝ እንጫወት ፎቶ ላኪልኝ እዚህ ውስጥ ገብተሽ
አጉል ስሜት ውስጥ ከገባሽ በዋላ
ወንዶች ሁላ አንድ ናቸው የማለት መብት የለሽም
የምሬነው የምልሽ በፍጹም የለሽም
መቼም ቢሆን ትኩረት መስጠት ያለብሽ ፍቅረኛ ካለሽ ለፍቅረኛሽ ከሌለሽ ደግሞ ፍቅረኛዬ ይሆናል ብለሽ ለምታስቢዉ ወንድ እንጂ የመጣዉን ወንድ ሁላ ፍቅረኛዬ ነው ብሎ ማሰብ መብት የለሽም አንቺ ፍቅር ከአንድ ሰው ጋር የምታስቢው እንጂ
ከህዝብ ጋር የምታቆይዉ አጀንዳ አይደለም
ተረዳሽኝ እና ጥፋቱ አንቺ ጋር ነው እራስሽን መርምሪ

ቅሬታ ካለሽ comment አለልሽ👍
HTML Embed Code:
2024/03/28 12:35:02
Back to Top