TG Telegram Group Link
Channel: Hawassa University Students' Information Center
Back to Bottom
Hawassa University Students' Information Center
Opportunity alert for Hawassa university students.
‼️Attention.‼️
This call is for students having the skill of developing logo Which means the one who is going to apply should consider this one.

Graphics designing and engineering students are highly adviced to apply
#CALL FOR APPLICATION 🔔

Join the Concerned Generation Movement as an #Ambassador for your university/college 🎓!

The Concerned Generation Movement, #CGM | 2024, which is initiated by The Inspired Ethiopian Youth Association, #IEYA, aims to cultivate an #CampusAmbassador for the Concerned Generation Movement-2024 at your university or Campus.

REQUIREMENTS
To become an official Ambassador you must meet the following criteria:

- Must have at least 2 years left before graduation
- Active participation in extracurricular activities in the University
- Commitment to take responsibility and drive change within your community
- Must be available for the May 23,24 and 25 event in Addis Ababa
👇👇
Titled ❝Concerned Generation Movement for Peace Building, Tourism and Climate Justice

📲If you are passionate about making a difference, apply now👇
https://forms.gle/6a4THU79Q14RaN9u5

#ConcernedGeneration #CGM2024 #Tourism #PeaceBuilding #ClimateJustice #wearehiring #Ambassadors #Presidents #JoinIEYA #globalmovement
የንግስት/ሞቲቴ ፉራ ታሪክ በመቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃርያን ህብረት በሀዋሳ ዩኒቨርሲት በቴያትር መልክ ሊቀርብ ነው።

ንግስት ፉራ ማናት?
በቀጣይ እንመለስበታለን!
Forwarded from 2016 GC_HU main campus
Color Day and 100 day Celebration at Hawassa University Main Campus


The celebration of the 100-day countdown and Color Day was a huge success at the main campus of Hawassa University on Friday, April 19th. The event was filled with music, color spraying on T-shirts, and a fun photo shooting program.

The atmosphere was cheerful and vibrant as students enjoyed the festivities. Memories were made as students danced to the music, took photos, and recorded videos to capture the joyful moments.

Thank you to everyone who participated and made the celebration a memorable one. Let's continue to spread positivity and joy as we count down to the upcoming events at our university.

Stay tuned for more exciting events and activities coming your way!

Join our official telegram channel using the link below 👇

https://hottg.com/GC2016_Hu

Main campus G.C committee
Forwarded from HU Charity Sector
----------------------- ሜሪ ጆይ -----------------------

ሚያዚያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መማክርት የበጎ አድራጎት ዘርፍ ከምክንያታዊ ባለራዕዮች ስብስብ RVC ጋር በመሆን በሀዋሳ የሚገኘውን የአረጋውያን መንከባከቢያ ማዕከል ሜሪ ጆይ ጎበኙ።

በጉብኝቱ ወቅት ከተከናወኑ ተግባራት መካከል ጊቢውን እና የማደሪያ ክፍሎችን የማጽዳት ስራ፡ የአረጋውያንን ልብስ ማጠብ፡ ጊቢውን ማስዋብ፡ ከአረጋውያን ጋር ጊዜ ማሳለፍ የሚጠቀሱ ናቸው።

በዚህ ተግባር አረጋውያን ደስ እንዳላቸው እና ይህ ተንባር መበረታታት እንዳለበትም ጭምር  በመግለጽ ከማይጠገበው ባርኮታቸው አካፍለውናል።

ርህራሄን በተግባር
| የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መማክርት የበጎ አራጎት ዘርፍ
@husccs
@husccs

#ኑ_የቆምንበትን_መሠረት_እንፈትሽ
#የተሻለ_ትውልድ_ለተሻለች_ኢትዮጵያ
#የምክንያታዊ_ባለራዕዮች_ስብስብ
@RvcClub
@RvcClub
ንግስት/ሞቲቴ ፉራ ማነች

ምንም እንኳን ባግባቡ የተሰነዱ የፅሁፍ መረጃዎችን እንደልብ ማግኘት ባይቻልም ንግስት ፉራ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ ዛሬም ድረስ ምትነሳ ስመ ገናና ንግስት መሆኗ ማየት ይቻላል። ምንጮች እንደሚያስረዱት ሞቲቴ ፉራ በ16ኛው ክፍለ ዘመን የነበረችና የሲዳማን ህዝብ በንግስትነት እንዳስተዳደረች የሚነገርላት ስትሆን በግዜው እንደሚታሰበው እንደሴት ብልህ ነገር አዋቂ ብቻም ሳትሆን እንደወንዶቹም አዳኝ ጠንካራ ድፍረትና ጀግንነትን የተላበሰች  ንግስት እንደነበረች ይነገራል። ቀድመን አንደጠቀስነው ምንም እንኳን በግዜው የተከተቡ ድርሳናትን ማግኘቱ ቢያዳግትም የሲዳማ ህዝብ በአፈ-ቃሉ ከልጅ ልጅ እያወሳ ከመጣው ታሪክ በተጨማሪ  አሁን በዘመናችን የተፃፉና የተቀመጡትን ድረሳናትና ማስረጃዎች (ለምሳሌ: የሲዳማ ህዝብ ታሪክ፣ ንግስት ፉራ --- መፅሃፍ) ዋቢ ስናረግ ንግስት ፉራ በንግግርና በአስተሳሰብ በልጦ በመገኘት የምታምን የሴቶችን የበታችነት ወይም መጎዳት ለማስቀረት ትሰራ የነበረች በዚህም ሀሳቧ የደገፏትን ማትነካ የሚቃወሟትን ደግሞ የምትቀጣ መሪ እንደነበረች መናገር ይቻላል።  ሞቲቴ ፉራ ሴቶች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ያልነጠረ ቅቤያቸውን፣ ያልተፈተል ጥጣቸውን፣ያልበሰል የጎመን ቅንጥሳቸውን ለባሎቻቸው እንዳያሳዩ ትመክር ነበር ይህም ቅቤው ሲነጥር ሲጣራ መጠኑ ያንሳል፣ ጥጡም ሲፈተል አንደቀድሞው ክምር አይሆንም፣ ጎመኑን ሲቀቀል ሙሽሽ ይላል ታድያ ባሎች ይህን ሲያዩ ያን ሁሉ የት አረግሽው እያሉ ያስጨንቋችኋል ከሚል ህሳቤ ነው።

ሞቲቴ ፉራ ወንዶችን ከሩቅ ቦታ ትኩስ ወተት አልባችሁ ሳይቀዘቅዝ አምጡልኝ፤ ከምድር ከፍ ከሰማይ ዝቅ ያለ ቤት ስሩልኝ፤  አንድ የፀጉር ዘለላን ስድስት ቦታ ሰንቃችሁ አምጡልኝ እና መሰል ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ለማሰብም ሚከብዱ ተግባራትን ታዝ እንደነበር ይነገራል። ይህንንና መሰል መረጃወችን በመጥቀስ ሞቲቴ ፉራ የሴቶችን አምባገነንነት ታስፋፋ ነበር የሚሉ የታሪክ ዘጋቢዎች ቢኖሩም  ንግስት ፉራ ሴቶች አቅማቸውን እንዲያወጡና ወንዶችም ይህን እንዲረዱ እንዲሁም እንዲቀበሉ ምታደርግና አንደ የትኛውም ገዢ መቅጣት አለብኝ ብላ ያሰበችው የምትቀጣ ያዘዘችሁም ትዕዛዝ ባይፈፀም እንኳን ብልሃት የታከለበት አሳማኝ መልስ ከተሰጣት ምህረትን የምታደርግ እንጂ ወንዶችን በሞላ ለመቅታት የወረደች ንግስት አልነበረችም ብለው ሚያስረዱ ብዙ  ምንጮችን እናገኛለን።

ሞቲቴ ፉራ በመጨረሻም አካሄዷን በሚቃወሙ    " አዋቂ" ሰዎች  በታሰበ ሴራ ቆርኬ ምትባለውን የዱር እንስሳ ስትጋልብ ህይወቷም ዘመኗም እንዳለፈ ቢነገርም ዛሬም ድረስ እናቶች ልጆቻቸውን እንዲህ እያሉ ስሟንም ታሪኳንም እያነሱ ያጫውቱበታል።

ኦሶ ሃዬ ሃዬ ፉራ ሜንቱ ቢሎ--- አኒ ዲ አፎማ
አፉ ኖሁ ይኖ---ቆርኬ ጊዲሲሴ
ቆሎ ውዲሲሴ --- ፉራ ጌርቹ ሺኖ
ፉራ ሺሁ ሺሞ ..... ይላሉ

ይህንንም እንጉርጉሮ አቻ ይሆናል ባልነው አማርኛ ስንተረጉመው:

ማሙ እሹሩሩ ማሙ እሹሩሩ
ፉራ የሴቶች ቁንጮ ካሉት በሃገሩ
አጋዘኗን ጭኖ ኮርቻ እንደፈረስ
አስጋለብኩኝ ብሎ አለባብሶ ግላስ
ፉራን ያስገደላት  አዋቂ ሰው ይነስ...


ባሁኑ ሰዓት ይህ የንግስት ፉራ ታሪክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ  በመቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃርያን ህብረት በቴያትር መልክ እየተሰራ ይገኛል።

በዚው አጋጣሚ ይህን በሲዳማ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ቦታ ያላትን የንግስት ፉራን ታሪክ የሚያወሳ ስራ የተሳካና ያማረ ይሆን ዘንድ የምትችሉ ሁሉ የcostume በተለይም የሲዳማ ባህላዊ አልባሳትን የማዋስ ድጋፍ እንድታደርጉልን ስንል በአክበወሮት እንጠይቃለን።

የሚከተሉትን የtelegram account ማናገር ይቻላል 👉 @zewdnssh @Beli1223

ይህ ደግሞ ይፋዊ የመቅረዝ የtelegram group ነው 👉 https://hottg.com/mekerezeactingstudents
HTML Embed Code:
2024/05/03 19:09:20
Back to Top